በደ/ግ/ም/ኢንስቲትዩት የአረካ ግንርና ምርምር ማዕከል የደቡብ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳሬክተር አግደዉ በቀለ(ደ/ር) አና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በማዕከሉ እየተሰሩ ያሉ የቴክኖሎጂ ማስተዋወቅና መነሻ ዘር ብዜት ሥራ መስክ ምልከታ ተደረገ ፡፡ የማዕከሉ አስተዳዳሪ በጥቅሉ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉትን ስራዎች በማመላከት ስራዎቹ በመስክ እንዲጎበኙ በማጋበዝ ማዕከሉ እያከናወነ ያለውን ልዩ ልዩ የእንሰት፣ የጎደሬ፣ የቦሎቄ፣ የጤፍ እና የስንዴ መነሻ ቴክኖሎጂ ዘር ብዜት እና ማሰተዋወቅ ምርምር ሥራዎችን ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳና ከቀበሌያት በተሳታፉ በለድረሻ አካላት እና የቀበሌ ሞዴል አርሶ አደሮች መስክ ጉብኝት ተደርጓል፡፡ ማዕከሉ በምርምር የተገኙ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የአከባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሰፊ ግብ ጥሎ እየተነቀሰቀሳ ሲሆን በአከባቢዉ የሞዴል ቴክኖሎጂ መንደር በመመሥረት ለአርሶ አደሩ የተሻሻለ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ተደረሽ እንዲሆኑ ማዕከሉ እየሠራ እንደሆነ ለማሳየተ ተችሏል ፡፡በመጨረሻም የመስክ ጉብኝቱ ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ይታቸዉን ውይይት በማድረግ ተጠናቋል፡፡